Home News World
World

ኢትዮጵያ በ9 ወራት 1.2 ሚሊዮን የውጭ ጎብኚዎችን አስተናገደች

April 3, 2026 2 weeks ago

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን በመሳብ ከ2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እና ሀገር ውስጥ ቱሪዝምም ከ30 ሚሊዮን በላይ የአካባቢ ተጓዦችን በማስተናገድ ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዳገኘች የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ።

ይህ እድገት ዘርፉን እያስተካከሉ ባሉ ሰፊ ማሻሻያዎች እና ዋና ዋና የልማት ተነሳሽነቶች ምክንያት እንደሆነ ሚኒስቴገልጸዋል።

የማስተዋወቂያ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተሾመ ተክሉ ለኢዜአ እንደተናገሩት የጎብኚዎች ቁጥር ቀጣይነት ያለው ጭማሪ ባለፉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ውስጥ የተተገበሩ ቀጣይነት ያላቸው ተሃድሶዎች ቀጥተኛ ውጤት ነው ሲሉ በለይም በኢትዮጵያ የበለፀገ የተፈጥሮ እና የባህል ሀብቶች፣ ጠንካራ የመንግስት ድጋፍ እና ግልጽ የረጅም ጊዜ የልማት ስትራቴጂ ትልቅ ድጋፍ ዳደረገ ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።

ለይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም መገለጫ ከፍ ለማድረግ እና ሰፊ እና ብዙም ጥቅም ላይ ያልዋሉ መዳረሻዎችን ለመክፈት የታለሙ እንደ ገበታ ለሸገር ፣ ገበታ ገር እና ገበታ ለትውልድ የሚሉ ተከታታይ ዋና ዋና ተነሳሽነቶችን በስኬት በመምራት በቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ ለውጥ እንዳመጣ አክለዋል

በተለይም በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የሚገኙ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የቱሪስት መዳረሻዎችን ኢላማ በማድረግ ገበታ ገር በሚለው ፕሮግራም ስር ለተጨማሪ እድገቶች መንገድ እንደከፈተ ገልጸዋል። በዋና ከተማዋም ውስጥ የወንዝ ዳርቻዎችን በማደስ፣ አረንጓዴ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን እና የመዝናኛ ቦታዎችን በመፍጠር ላይ ያተኮረው ሸገርን ማስዋብ ፕሮጀክት የራሱ የሆነ ተጽዕኖ እንዳመጣም ሚኒስቴገልጸዋል።

መንግስት እንደ የሃረር ጎል እና የፋሲል ግንብ ያሉ ታሪካዊ ቦታዎችን መልሶ ማቋቋም እና መጠበቅ ላይ ቅድሚያ በመስጠት የባህል ቅርሶችን በመጠበቅ ለአለም አቀፍ ጎብኚዎች ያላቸውን ማራኪነት በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። በተመሳሳይም መልኩ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችን እና ዝግጅቶችን የማስተናገድ አቅሟን በማደግ የቱሪዝም ፍሰቱ የበለጠ እንዲያድግ ተጽዕኖ እንዳመጣም ሚኒስቴ አክለዋል

እነዚህ የተጣመሩ ጥረቶች አገሪቱን በአፍሪካ እየጨመረ ከሚሄደው ተወዳዳሪ የቱሪዝም መዳረሻዎች አንዷ አድርጋ አስቀምጧታል ሲሉ ሚኒስቴገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በ2026 በዓለም ላይ በፍጥነት እያደጉ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች አንዷ ስትሆን፣ በ2025 ዓለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻዎች በ15 በመቶ ጨምራለች ሲሉ የቅርብ ጊዜ ሪፖርቶች አመልክተዋል።

Scroll to Top