የጅማ ዩኒቨርሲቲ ከቦይንግ ጋር የአየር በረራ ስልጠናን ሊያሰፋ ነው
የጂማ ዩኒቨርሲቲ በአፍሪካ የሰለጠኑ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ፍላጎት እየጨመረ በመምጣቱ ከቦይንግ ጋር የረጅም ጊዜ አጋርነት በማድረግ የአቪዬሽን ሳይንስ እና የኤሮስፔስ ምህንድስና ስልጠናውን ለማስፋት ተዘጋጅቷል።
ስምምነቱ የዩኒቨርሲቲውን የአቪዬሽን ሳይንስ እና የኤሮስፔስ ምህንድስና አካዳሚ በመሠረተ ልማት ማሻሻያዎች፣ በሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያ እና በማህበረሰብ ተሳትፎ ፕሮግራሞች በመደገፍ ለወደፊቱ የአየር በረራ የላቀ ማዕከል መሰረት እንደሚፈጥር ይጠበቃል።
ሁለቱ ወገኖች በ2026 የመማሪያ ክፍሎችን ማዘመን፣ መምህራንን ማሰልጠን እና ተማሪዎችን ትኩረት ያደረጉ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት እና መተግበር ላይ ለማተኮር አቅደዋል። በተጨማሪም ሽርክናው የኤሮስፔስ ፈጠራ ፈተናን ጨምሮ የተማሪዎችን ፕሮቶታይፕ ለመደገፍ ቴክኒካዊ መሳሪያዎችን እና ቁሳቁሶችን ማቅረብ ላይም ያተኩራል ተብሏል።
በቦይንግ የአፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ሄኖክ ተፈራ ሻውል የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፍ በአየር ማረፊያ ልማት እና በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእድገት ስትራቴጂ በመመራት ቀጣይነት ባለው የማስፋፊያ ዘመን ውስጥ እየገባ ነው ብለዋል። አክለዉም የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ አመቱን ሲያከብር እና የበረራ፣ የኔትወርክ እና የጭነት አቅሙን በ2035 ራዕይ ስር ሲያሰፋ፣ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ለከፍተኛ እድገት ዝግጁ እየሆነ መምጣቱን ገልፀዉ ከጂማ ዩኒቨርሲቲ ጋር ያለን ሽርክና የተሰጥኦ መስመሩ ከዚያ እድገት ጋር እንዲጣጣም እንደሚያረግ ገልፀዋል።
በመቀጠልም የጂማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አቶ ጀማል አባፊታ እንዳሉት ትብብሩ የአካዳሚክ ፕሮግራሞችን ከኢንዱስትሪ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም እና ተቋሙን በአፍሪካ የአቪዬሽን እና የኤሮስፔስ ስልጠና ግንባር ቀደም ማዕከል ለማድረግ የተነደፈ ነው ብለዋል።
ኩባንያው የምህንድስና ሥርዓተ ትምህርቶችን ለማጠናከር እና የተሰጥኦ ማዕከላት ለመገንባት በአፍሪካ ውስጥ ባሉ የዩኒቨርሲቲ ሽርክናዎች ላይ ኢንቨስት ለማድረግ የተቋቋመ ስርዓት ያለዉ ሲሆን የአፍሪካ ተነሳሽነቶቹ የረጅም ጊዜ የአካዳሚክ ትብብሮችን እና የእርዳታ ድጋፎችን ያካትታል።
ቦይንግ የአየር ጉዞ እና የጭነት አገልግሎቶች ፍላጎት እየጨመረ በመምጣቱ የአፍሪካ አየር መንገዶች በሚቀጥሉት ሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ 1,205 አዳዲስ አውሮፕላኖች እና ወደ 74,000 የሚጠጉ ተጨማሪ የአቪዬሽን ሰራተኞች እንደሚያስፈልጉ ይገምታል።